+251118132191

contact@mint.gov.et

Font Awesome Icons
Fixed Header Menu Example

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከማስተርካርድ ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል የአጋርነት ፊርማ ሥነሥርዓት አካሄደ።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ እና የምስራቅ አፍሪካ ማስተርካርድ ኮርፖሬሽን ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ሸህሪያር አሊ (Mr. Shehryar Ali, Country Manager East Africa-Mastercard) ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የአጋርነት የምስክር ወረቀት ፊርማ ሥነሥርዓት ተካሂዷል፡፡

መቀመጫውን ምስራቅ አፍሪካ ላይ ያደረገ ማስተርካርድ ኮርፖሬሽን የግሎባል ፔይመንት ኔትዎርክ ግብይቶች ስነምዳርን በማመቻቸት (Enabling Global Payment Network Transactions) ዓለም አቀፍ ካርዶችን መጠቀም የሚያስችል በሰው ሠራሽ አስተውሎት የተደገፈ የአቅም ግንባታ ሥራዎች ላይ በአጋርነት እየሠራ ያለ ዓለም አቀፍ ተቋም ነው፡፡

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ በሀገራችን ፈጣን የሆነ ሁለንተናዊ እድገት ለማስመዝገብ በዲጂታል ዘርፉ ላይ ዘርፈ ብዙ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን አስገንዝበዋል።

ዘመኑን የዋጀ የዲጂታል ስነምህዳር መገንባት ዓላማችን ነው ያሉት ሚኒስትሩ በሀገራችን የዲጂታል ዘርፉን ለማሳደግ ከሀገር ውስጥና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብርና በአጋርነት የሚሰሩ ስራዎች ትኩረታችን ናቸው ብለዋል።

የምስራቅ አፍሪካ ማስተርካርድ ኮርፖሬሽን ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ሸህሪያር አሊ (Mr. Shehryar Ali, Country Manager East Africa-Mastercard) በኢትዮጵያ የዲጂታል ዘርፍ ላይ በአጋርነት ለመስራት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል።

የአጋርነት የምስክር ወረቀት ፊርማው ዋና ትኩረቱ የዲጂታል ቱሪዝም በኢትዮጵያ የዲጂታል ክፍያዎች ለማበረታታትና ለማቀላጠፍ ሲሆን ዲጂታል ፋይናንሺያል ስርአት ሥነምህዳርን ማስፋትና ከአለማቀፍ ስርአት ጋር የማስተሳሰር አጋርነት ከኢትዮጵያ ተቋሞች ጋር ተያይዞ የአቅም ግንባታ ሥራዎችን ለመስራት ፕሮጀክቱን በይፋ ለማስጀመርና ለማስተዋወቅ ነው።

የአጋርነት የምስክር ወረቀት ፊርማ ስነ ሥርዓቱ ላይ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሙሉቀን ቀሬ፣ ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች እና ከማስተርካርድ የምስራቅ አፍሪካ ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡

በብዛት የተጎበኙ

News Card Example

መንግስት የቀድሞው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርን በማዋሃድ     በ2011 ዓ.ም  የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር  ተቋቋመ፡፡

የትኩረት መስኮች

  • ምርምር
  • ኢኖቬሽን
  • የቴክኖሎጂ ሽግግር
  • ዲጂታላይዜሽን

ያግኙን

  • ስልክ: +251118132191
  • ኢሜል: contact@mint.gov.et
  • ድረ-ገጽ: www.mint.gov.et

የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገጾች

Font Awesome Icons

©2024 MINT መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ከእርምጃ ወደ ሩጫ