+251118132191
contact@mint.gov.et
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በኮምቦልቻ ከተማ የገነባቸውን የአቅመደካማ ቤቶች አጠናቆ አስረከበ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት በተለያዩ ክልሎች ከሚያደርገው የችግኝ ተከላና የአቅመ ደካማ ቤቶች እድሳት መርሃ ግብር ውስጥ በኮምቦልቻ ከተማ በአዲስ መልክ የገነባቸውን 7 የመኖሪያ ቤትች በማጠናቀቅ የከተማው ከፍተኛ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ለአቅመደካሞች ቁልፍ አስረከቡ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ የሀገራችንን የኢኮኖሚ እድገት ለማጎልበት በምናደርገው ርብርብ ውስጥ የአቅመ ደካሞችን ህይወት የኑሮ ሁኔታ ሊደግፉ በሚችሉ ዘርፎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበት ገልፀዋል።
የተሰሩት የአቅመ ደካሞች ቤቶችን ሰርተን ስናስረክብ ቀጣይ ሌሎች ከዚህ በላይ መስራት እንዳለብን አቅም ከመሆን ባሻገር ሌሎች ተቋማትና ባለሀብቶች እንዲህ ባሉ ዘርፍ ላይ የድርሻቸውን እንዲወጡ መነሻ ሊሆኑ እንደሚችሉ አስገንዝበዋል።
የስራችን ውጤት የሚለካው ለዜጎቻችን ባደረግነው ተጨባጭ ውጤት ነው ያሉት ክቡር ሚኒስትሩ በክረምት ካከናወናቸው መርሀ ግብር ውስጥ የተጀመሩ የአቅመ ደካማ የቤቶች ግንባታ ስራዎች በዚህ መልኩ ተጠናቀው ውጤት ላይ ደርሰው ስናያቸው በሁላችንም ዘንድ ከፍተኛ እርካታን ይፈጥራሉ ብለዋል።
የኮምቦልቻ ከተማ ከንቲባ ክቡር መሀመድ አሚን በአለም ላይ ብዙ ሀገሮች ጂዲፒያቸውን የሚያገኙት ከከተሞቻቸው ሲሆን ይህንን ውጤት ለማምጣት በሀገራችን በማደግ ላይ ያሉ የከተሞቻችንን ውስብስብ ችግሮች ለመፍታትና ደረጃቸውን ለማሳደግ ሁሉን ባሳተፈ መልኩ መሰራት እንዳለበት ገልፀዋል።
መንግስት ከተሞችን ለማሳደግ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ አየሰራበት ያለውን እቅድ ለማሳካት አሮጌ ቤቶችን እና ሌሎች ሰው ተኮር በሆኑ ልማቶች ላይ ከተለያዩ አካላት ጋር በትብብር እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።
በክረምት መረሀ ግብር በተለያዩ ክልሎች እየተከናወኑ ያሉ የችግኝ ተከላ፣ መማር ላልቻሉ ተማሪዎች የቁሳቁስ ድጋፍ፣ የአቅመ ደካሞች ቤቶች እድሳትና በአዲስ መልክ ሰርቶ ከማስረከብ ባለፈ ከተሞችን በዲጂታል ለማዘመን የሚደረጉ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተጠቁሟል። በዚሁም መሠረት የኮምቦልቻ ከተማ፣ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ተቋም፣ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኮሌጅ የኮምቦልቻ ከተማን የዲጂታል አድራሻ ስርአት ለማልማት የሶስትዮሽ ስምምነት የፊርማ ስነስርአትም የተካሄደ ሲሆን በጂአይኤስ እንዲሁም በማዳበሪያ አዘገጃጀት ስልጠና ለወሰዱ ወጣቶች የሰርተፊኬት ሽልማት ተሰጥቷል።
Most Viewed News
ትኩስ ዜና
41st Regular Council of Ministers Meeting Resolutions The council of ministers discussed and passed a decision on various issues at the 41st regular meeting today.
41st Regular Council of Ministers Meeting Resolutions The council of ministers discussed and passed a decision on various issues at the 41st ...
Read More5 Million Coders Professional Training
Register here to benefit from free online training opportunities through the Five Million Ethiopian Coders Initiative to develop basic coding ...
Read More5 million Ethiopian coders
The "5 million Ethiopian coders" initiative is a program that will help our youth to have the appropriate digital skills and create jobs and ...
Read More780 thousand citizens are undergoing five million Ethio Coders training –H.E Minister Dr. Belete Molla
Minister of Innovation and Technology Belete Molla (Dr) stated that in the 5 million Ethiopians coders initiative, 780 thousand citizens are ...
Read MoreA delegation from Kagool,
A delegation from Kagool, a leading global data and analytics group, and Micro Tech London visited Ethiopia to assess opportunities in the ...
Read MoreThe government merged the former Ministry of Science and Technology and the Ministry of Communication and Information Technology to form the Ministry of Innovation and Technology in 2019.
Focus Areas
- Research
- Innovation
- Technology Transfer
- Digitalization
Contact
- Tell: +251118132191
- Email: contact@mint.gov.et
- Website: www.mint.gov.et
Connect to MInT