+251118132191
contact@mint.gov.et
የ "5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ" ኢኒሼቲቭ ወጣቶቻችን ተገቢው የዲጂታል ክህሎት እንዲኖራቸው በማድረግ ስራ እና ሀብትን በመፍጠር የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን በስፋት ለማቀጣጠል የሚረዳ ፕሮግራም ነው።ዶ/ር በለጠ ሞላ
አምሰት ሚሊዮን ዜጎች የዲጂታል ቴክኖሎጂ ስልጠና ተጠቃሚ የሚሆኑበት የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቪን
በዛሬው እለት በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ይፋ ሆኗል።
በመርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዶ/ር በለጠ ሞላ የ "5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ" ኢኒሼቲቭ ወጣቶቻችን ተገቢው የዲጂታል ክህሎት እንዲኖራቸው በማድረግ ስራ እና ሀብትን በመፍጠር የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን በስፋት ለማቀጣጠል የሚረዳ ፕሮግራም ነው ብለዋል።
ሚኒስትሩ ዛሬ፣ ቴክኖሎጂ የስራ መሳሪያ ብቻ ሳይሆን የለውጥ አራማጅ የሆነበት አዲስ የዘመን ምዕራፍ ላይ ደርሰናል ያሉት ሚኒስትሩ የነገዋን ኢትዮጵያ የሚቀርፁት የፈጠራ ባለሙያዎች እና ተመራማሪዎች ናቸው ብለዋል።።
የኢትዮ ኮደርስ ፕሮግራም ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን በዲጂታል ስነ ምህዳሩ ውስጥ በንቃት እንዲሳተፉ የሚያስችላቸውን ክህሎትና እውቀት በማስታጠቅ አዳዲስ እድሎች እንዲፈጠርላቸው እና ሀገራችን በቴክኖሎጂው መስክ ወደፊት እንድትገሰግስ በር የሚከፍት መሆኑንም ሚንስትሩ አንስተዋል።
የኢትዮኮደርስ ፕሮግራም ወጣቶቻችንን ለማብቃት፣ ፈጠራን ለማጎልበት እና የዲጂታል ዘመንን ግዙፍ አቅም ለመጠቀም መንግስት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው ብለዋል።
የዲጂታል ኢትዮጵያን ለማረጋገጥ ወሳኝ ከሆኑት መሰረቶች አንዱ የዲጂታል ስነ ምህዳሩን መገንባት እና የዲጂታል ክህሎት በመሆኑ በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ውስጥ ከኢኮኖሚው ለመጠቀም ሆነ አገልግሎት ለማቅረብ ወሳኝ መነሻ በመሆኑ የ 5 ሚሊየን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢኒሼቲቨ የወጣቶቻችንን የዲጂታል ክህሎት ለማሳደግ አንዱ ምላሽ ሆኖ መምጣቱን ተናግረዋል።
"ኮድ ማድረግ የኮድ መስመሮችን መጻፍ ብቻ አይደለም። ኮድ ማድረግ ችግር ፈቺ፣ ሂሳዊ አስተሳሰብ እና ፈጠራ ነው።"ያሉት ሚኒስትሩ ወጣቶቻችን የኮዲንግ ክህሎት እንዲኖራቸው ስናደርግ ሰፊ ወደ ሆነው የዲጂታል አለም በልበ ሙሉነት በመቀላቀል ሌሎች የፈጠሩዋቸውን አፕሊኪሽኖች መጠቀምም ብቻ ሳይሆን በቀጣይ አገርን የሚጠቅም እና የሰው ልጆችን ህይወት የሚያቀሉ በርካታ አፕሊኪሽኖችን በራሳቸው ማልማት እንዲችሉ መንገዱ እየተመቻቸላቸው እንደሆነ መገንዘብ ያስፈልጋል ብለዋል።
Most Viewed News
ትኩስ ዜና
41st Regular Council of Ministers Meeting Resolutions The council of ministers discussed and passed a decision on various issues at the 41st regular meeting today.
41st Regular Council of Ministers Meeting Resolutions The council of ministers discussed and passed a decision on various issues at the 41st ...
Read More5 Million Coders Professional Training
Register here to benefit from free online training opportunities through the Five Million Ethiopian Coders Initiative to develop basic coding ...
Read More5 million Ethiopian coders
The "5 million Ethiopian coders" initiative is a program that will help our youth to have the appropriate digital skills and create jobs and ...
Read More780 thousand citizens are undergoing five million Ethio Coders training –H.E Minister Dr. Belete Molla
Minister of Innovation and Technology Belete Molla (Dr) stated that in the 5 million Ethiopians coders initiative, 780 thousand citizens are ...
Read MoreA delegation from Kagool,
A delegation from Kagool, a leading global data and analytics group, and Micro Tech London visited Ethiopia to assess opportunities in the ...
Read MoreThe government merged the former Ministry of Science and Technology and the Ministry of Communication and Information Technology to form the Ministry of Innovation and Technology in 2019.
Focus Areas
- Research
- Innovation
- Technology Transfer
- Digitalization
Contact
- Tell: +251118132191
- Email: contact@mint.gov.et
- Website: www.mint.gov.et
Connect to MInT