+251118132191

contact@mint.gov.et

Font Awesome Icons
Fixed Header Menu Example

ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፍ ጥሩ አፈፃፀም ካላቸው ሀገራት መካከል ነች

25ኛው የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ የፋይናንስ ሚኒስትሮች ስብሰባ በኬኒያ ናይሮቢ ተካሂዷል፡፡

በመድረኩ የተሳተፉ ሚኒስትሮች ዲጂታል ትስስርን ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል፡፡

በፈረንጆቹ 2023 ስለፀደቀው የዲጂታል ውህደት እና የፖሊሲ ማዕቀፍ ሚኒስትሮች ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በዚህም ሀገራት ጥሩ አፈጻጸም በማስመዝገብ ላይ መሆናቸው የተመላከተ ሲሆን፤ ኢትዮጵያ ጥሩ አፈፃፀም ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ነች ተብሏል፡፡

በምክክሩ የተሳተፉት የገንዘብ ሚኒስትር ዴዔታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በዲጂታል ውህደት እያስመዘገበች ያለችውን ዕድገት ገልፀዋል፡፡

ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፍ የቴሌኮም ዘርፎችን ነፃ ማድረግ፣ የግል መረጃ ጥበቃ እና የሳይበር ደህንነት ህጎችን በማውጣት በርካታ ተግባራት ማከናወኗን ጠቁመዋል።

ከ19 ሚሊየን በላይ ዜጎች በዲጂታል መታወቂያ ስርዓት በመመዝገብ ውጤት ማምጣት መቻሉን ማብራራታቸውን ሚኒስቴሩ ለፋና ዲጂታል በላከው መረጃ አመላክቷል።

በብዛት የተጎበኙ

News Card Example

መንግስት የቀድሞው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርን በማዋሃድ     በ2011 ዓ.ም  የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር  ተቋቋመ፡፡

የትኩረት መስኮች

  • ምርምር
  • ኢኖቬሽን
  • የቴክኖሎጂ ሽግግር
  • ዲጂታላይዜሽን

ያግኙን

  • ስልክ: +251118132191
  • ኢሜል: contact@mint.gov.et
  • ድረ-ገጽ: www.mint.gov.et

የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገጾች

Font Awesome Icons

©2024 MINT መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ከእርምጃ ወደ ሩጫ