+251118132191

contact@mint.gov.et

Font Awesome Icons
Fixed Header Menu Example

የመሰረተ ልማት መስፋፋት ዜጎች በስልክ ብቻ በቀላሉ መረጃ ማግኘት እንዲችሉ አድርጓል

የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት መስፋፋት ዜጎች በስማርት ስልክ እና በኢንተርኔት ብቻ በቀላሉ የሚፈልጉትን መረጃ ማግኘት እንዲቻል ማድረጉን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሚኒስትሩ ከፍተኛ አማካሪ አብዮት ባዩ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡

ኢቢሲ በራሱ አቅም ያበለፀገውን መተግበሪያ በይፋ ባስመረቀበት ወቅት አብዮት ባዩ (ዶ/ር) "ጠንካራ ሀገር ለመገንባት የዲጂታል ሚዲያው ሚና ምንድን ነው" በሚል በተዘጋጀው የፓናል ውይይት ላይ የመነሻ ፅሁፍ አቅርበዋል፡፡

አብዮት ባዩ (ዶ/ር) በማብራሪያቸው፤ የኢንተርኔት ተደራሽነት መስፋፋት ሚዲያዎች እንዲተጉ እና ተወዳዳሪነታቸው እንዲጨምር አድርጓል ብለዋል፡፡

የዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ኢትዮ ቴሌኮም መሰረታዊ የሚባሉትን ሲስተሞች በሀገራችን እንዲኖሩ በማድረግ ከፍተኛ ስራ አከናውኗል ያሉት አቶ አብዮት፤ የኔትዎርክ ሽፋኑ 99.4 በመቶ መድረሱን ገልፀዋል፡፡

ሰው በሚኖርበት ማናቸውም የሀገራችን ክፍል ብንጓዝ አስተማማኝ የሆነ የኔትወርክ አገልግሎት ማግኘት የሚያስችል ሲስተም መገንባት ተችሏል ሲሉም ጠቅሰዋል፡፡

የመሰረተ ልማት መስፋፋት ዜጎች በስልክ ብቻ በቀላሉ መረጃ ማግኘት እንዲችሉ ማድረጉን ያነሱት አቶ አብዮት፤ ኢቢሲ ይህን እድል በመጠቀም በራስ አቅም ያበለፀው የዲጂታል መተግበሪያ ወደ ብዙዎች ለመድረስ እንደሚያችለው ተናግረዋል፡፡

በብዛት የተጎበኙ

News Card Example

መንግስት የቀድሞው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርን በማዋሃድ     በ2011 ዓ.ም  የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር  ተቋቋመ፡፡

የትኩረት መስኮች

  • ምርምር
  • ኢኖቬሽን
  • የቴክኖሎጂ ሽግግር
  • ዲጂታላይዜሽን

ያግኙን

  • ስልክ: +251118132191
  • ኢሜል: contact@mint.gov.et
  • ድረ-ገጽ: www.mint.gov.et

የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገጾች

Font Awesome Icons

©2024 MINT መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ከእርምጃ ወደ ሩጫ