+251118132191
contact@mint.gov.et
የቤት አስተዳደር ዘርፍን ዲጂታላይዝ ለማድረግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ምክክር ተካሂዷል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ጋር የቤት አስተዳደሩን ዘርፍ የአሰራር ስርዓት በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማዘመን ያለመ ነው።
ምክክሩ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ይሹሩን ዓለማየሁ እና የሚኒቴሩ አመራሮች በፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በመገኘት የተካሄደ ሲሆን ተቋሙን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎችንም ጎብኝተዋል።
በተካሄደው ምክክር ላይ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ይሹሩን ዓለማየሁ ኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ለማሳካት ሁሉም ተቋማት ከዘመኑ ጋር የሚሄድ፣ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያረጋግጥ በሆነ መልኩ አገልግሎታቸውን በ ዲጂታል ስርዓት መስጠት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
አሰራሮችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማዘመን የውዴታ ግዴታ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው ተቋማት ሁለንተናዊ ስራዎቻቸውን ለማዘመን የሚያደርጉትን ጥረት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በቅርበት ሆኖ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልፀዋል።
የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የቤቶችና ይዞታዎች ማስከበርና ማከራየት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጌቱ ዘውዴ የተቋሙ ስራዎችን ዲጂታላይዝ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ስራዎች መሰራታቸውን አብራርተዋል።
አክለውም የቤት አስተዳደር ዘርፉን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማዘመንና የተሳለጠ የአሰራር ስራዓቱ ለመዘርጋት ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በትብብር ለመስራትና ድጋፍ እንዲደረግላቸው እንደሚፈልጉ ገልፀዋል።
በብዛት የተጎበኙ
መንግስት የቀድሞው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርን በማዋሃድ በ2011 ዓ.ም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተቋቋመ፡፡
የትኩረት መስኮች
- ምርምር
- ኢኖቬሽን
- የቴክኖሎጂ ሽግግር
- ዲጂታላይዜሽን
ያግኙን
- ስልክ: +251118132191
- ኢሜል: contact@mint.gov.et
- ድረ-ገጽ: www.mint.gov.et
የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገጾች