+251118132191

contact@mint.gov.et

Font Awesome Icons
Fixed Header Menu Example

የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከዋና መስርያ ቤት እስከ ወረዳ የሚገኙ 367 ባለሙያዎች የ5 ሚሊዮን ኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወስደው ማጠናቀቃቸውን አስታወቀ።

ኤጄንሲው በዛሬው እለት ስልጠናቸውን ላጠናቀቁ 127 ባለሞያዎች የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ይሽሩን አለማየሁ እና በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ-አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በተገኙበት እውቅና ሰጥቷል።

በዝግጅቱ ላይ ኤጀንሲው የተቀመጠውን ሃገራዊ አቅጣጫ በተደራጀ መልኩ መምራቱን ያመሰገኑት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ዶ/ር ይሽሩን አለማየሁ ሌሎች ክልሎች እንደ ሃገር የአዲስ አበባ ከተማ አርዓያነት ሊከተሉ እንደሚገባ አንስተዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ-አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ የስልጠናው ዋና ግብ ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚችል ብቁ ሰራተኛ መፍጠር መሆኑ ታውቆ ሰልጣኞች ክህሎቱን ወደ ተግባር እንዲቀይሩ አፅንዖት ሰጥተዋል።

ባሉበት ሆነው በነፃ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ፣ በዳታ ሳይንስ ፣ በዌብ ፕሮግራሚንግ እና በአንድሮይድ ማበልፀግ ዙርያ የተዘጋጁ ነፃ የኦንላይን ስልጠናዎችን ለመውሰይ በ https://ethiocoders.et/ ላይ ይመዝገቡ።

በብዛት የተጎበኙ

News Card Example

መንግስት የቀድሞው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርን በማዋሃድ     በ2011 ዓ.ም  የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር  ተቋቋመ፡፡

የትኩረት መስኮች

  • ምርምር
  • ኢኖቬሽን
  • የቴክኖሎጂ ሽግግር
  • ዲጂታላይዜሽን

ያግኙን

  • ስልክ: +251118132191
  • ኢሜል: contact@mint.gov.et
  • ድረ-ገጽ: www.mint.gov.et

የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገጾች

Font Awesome Icons

©2024 MINT መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ከእርምጃ ወደ ሩጫ