+251118132191

contact@mint.gov.et

Font Awesome Icons
Fixed Header Menu Example

የኢትዮ ኮደሮች ስልጠና ያጠናቀቁ ከ270 ሺህ በላይ ወጣቶች የምስክር ወረቀት ወስደዋል

በ5 ሚሊየን የኢትዮጵያ ኮደሮች ፕሮግራም እስከ አሁን ከ270 ሺህ የሚልቁ ወጣቶች ሥልጠናቸውን በማጠናቀቅ የምስክር ወረቀት መውሰዳቸው ተገለጸ፡፡

በመላ ሀገሪቱ ባለፉት 10 ወራት ከ800 ሺህ በላይ ወጣቶች ተመዝግበው ስልጠናቸውን በመከታተል ላይ እንደሚገኙ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር አማካሪ አብዮት ባዩ (ዶ/ር) ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡

ከእነዚህ መካከል ከ200 ሺህ የሚልቁት በመሠረታዊ ፕሮግራሚንግ፣ ከ235 ሺህ በላይ በዳታ ሣይንስ፣ ከ220 ሺህ በላይ በአንድሮይድ ፕሮግራሚንግ እንዲሁም ከ125 ሺህ በላይ ደግሞ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ እየሰለጠኑ እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡

በሌላ በኩል ከ270 ሺህ በላይ ወጣቶች ስልጠናቸውን በማጠናቀቅ የምስክር ወረቀት መውሰዳቸውን ገልጸዋል፡፡

የ5 ሚሊየን የኢትዮጵያ ኮደሮች ፕሮግራም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን መሠረት በማድረግ መቀረጹንም አስረድተዋል፡፡

ይህም ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የለሙትን መተግበሪያዎች ተጠቅሞ እሴት የሚፈጥር እና በሂደትም መተግበሪያዎችን የሚያለማ እና የዲጂታል መሠረተ ልማቶችን የሚያሥተዳድር የሰው ኃይል እንዲኖረን ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል፡፡

በብዛት የተጎበኙ

News Card Example

መንግስት የቀድሞው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርን በማዋሃድ     በ2011 ዓ.ም  የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር  ተቋቋመ፡፡

የትኩረት መስኮች

  • ምርምር
  • ኢኖቬሽን
  • የቴክኖሎጂ ሽግግር
  • ዲጂታላይዜሽን

ያግኙን

  • ስልክ: +251118132191
  • ኢሜል: contact@mint.gov.et
  • ድረ-ገጽ: www.mint.gov.et

የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገጾች

Font Awesome Icons

©2024 MINT መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ከእርምጃ ወደ ሩጫ