+251118132191
contact@mint.gov.et
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽንን መሰረት ካደረጉ የሙያ ማህበራት ጋር በሀገራዊ የምርምርና ልማት አሰራር ሥርዓት ዙርያ ውይይት አካሂዷል፡፡
በውይይቱ ላይ በሚኒስቴሩ የሀገራዊ ምርምር ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሃብታሙ አበራ ምርምር፣የቴክኖሎጂ ሽግግርና ልማት ላይ በትኩረት መስራት በዘርፉ ተወዳዳሪ የሰው ሀይል ለማልማትና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት ፣ሳይንሳዊ መንገድን የተከተለ እና በማስረጃ የተደገፈ ውሳኔ ለመስጠት እንዲሁም የተለያዩ ፖሊሲዎችን እና ስትራቴጂዎችን ቀርጾ ተግባራዊ ለማድረግ አስፈላጊ ነው ብለዋል።
የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ልማት ሥራዎች የዓለማችን አንገብጋቢ ችግሮችን ለመፍታት ቁልፍ መሳሪያ በመሆናቸው የ2030 ዘላቂ የልማት ግቦችን እንዲሁም የአፍሪካ አጀንዳ 2063ን ለማሳካት ወሳኝ ድርሻ እንዳላቸውም በመድረኩ ተነስቷል፡፡
የሳይንስ፣ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ፓሊሲ የዘርፉን ስነ-ምህዳር ውጤታማ ለማድረግ በሚያስችል መልኩ መዘጋጀቱ የተገለጸ ሲሆን ፖሊሲውን ውጤታማ ለማድረግ የበርካታ ባለ ድርሻ አካላትን ንቁ ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ የግሉ ዘርፍ የሙያ ማህበራት ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው በመገንዘብ ለውጤታማነቱ የበኩላቸውን እንዲያበረክቱ ተጠቁሟል፡፡
በመድረኩም ብሄራዊ የምርምርና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በብዛት የተጎበኙ
መንግስት የቀድሞው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርን በማዋሃድ በ2011 ዓ.ም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተቋቋመ፡፡
የትኩረት መስኮች
- ምርምር
- ኢኖቬሽን
- የቴክኖሎጂ ሽግግር
- ዲጂታላይዜሽን
ያግኙን
- ስልክ: +251118132191
- ኢሜል: contact@mint.gov.et
- ድረ-ገጽ: www.mint.gov.et
የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገጾች